የኔፔይ ፋይናንሺያል ቴክኖሎጂስ ኃ/የተ/የግ/ማ በ2015 እ.ኤ.አ በ7 ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የተመሰረተ ድርጅት ሲሆን ዋና አላማው በፋይናንስ ቴክኖሎጂው ዘርፍ ለውጥ ፈጣሪ የሆኑ የተለያዩ መተግበሪያዎችንን በመስራት የመሪነት ሚናውን መጫወትና የሃገራችንን የፋይናንስ ኢንዱስትሪ አንድ እርምጃ ወደፊት ማራመድ ነው::
ድርጅታችን በፋይናንስ ቴክኖሎጂ አገልግሎት ዘርፍ ላይ እየሰራ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ውስጥ እየሰሩ ላሉ የንግድ ተቋማት ፈጣን ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ቀላል የሆነ የኦንላይን መክፍያ መተግበሪያን ለገበያው እያስተዋወቅ ይገኛል::